وَيْلٌۭ لِّكُلِّ هُمَزَةٍۢ لُّمَزَةٍ
ለሃሜተኛ ለዘላፊ ሁሉ ወዮለት፡፡
1
ጁዝ 30ገጽ 601
ጁዝ 30ገጽ 601
አጥላይው · 9 አንቀጾች
ሱራ 104 · መካዊ
وَيْلٌۭ لِّكُلِّ هُمَزَةٍۢ لُّمَزَةٍ
ለሃሜተኛ ለዘላፊ ሁሉ ወዮለት፡፡
ٱلَّذِى جَمَعَ مَالًۭا وَعَدَّدَهُۥ
ለዚያ ገንዘብን የሰበሰበና የቆጣጠረው (ያደለበውም) ለኾነ ፤(ወዮለት)፡፡
يَحْسَبُ أَنَّ مَالَهُۥٓ أَخْلَدَهُۥ
ገንዘቡ የሚያዘወትረው መኾኑን ያስባል፡፡
كَلَّا ۖ لَيُنۢبَذَنَّ فِى ٱلْحُطَمَةِ
ይከልከል፤ በሰባሪይቱ (እሳት) ውስጥ በእርግጥ ይጣላል፡፡
وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا ٱلْحُطَمَةُ
ሰባሪይቱም ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ?
نَارُ ٱللَّهِ ٱلْمُوقَدَةُ
የተነደደችው የአላህ እሳት ናት፡፡
ٱلَّتِى تَطَّلِعُ عَلَى ٱلْأَفْـِٔدَةِ
ያቺ በልቦች ላይ የምትዘልቅ የኾነችው፡፡
إِنَّهَا عَلَيْهِم مُّؤْصَدَةٌۭ
እርሷ በእርግጥ በእነርሱ ላይ የተዘጋጀች ናት፡፡
فِى عَمَدٍۢ مُّمَدَّدَةٍۭ
በተዘረጋች አዕማድ ውስጥ (የተዘጋች ናት)፡፡