LogoQuranEthiopia.com

ሱራ 36 · መካዊ

يسٓ

ያሲን

ያሲን · 83 አንቀጾች

۞

يسٓ

የ.ሰ.(ያ ሲን)

1
ጁዝ 22ገጽ 440

وَٱلْقُرْءَانِ ٱلْحَكِيمِ

ጥበብ በተመላበት ቁርኣን እምላለሁ፡፡

2
ጁዝ 22ገጽ 440

إِنَّكَ لَمِنَ ٱلْمُرْسَلِينَ

አንተ በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነህ፡፡

3
ጁዝ 22ገጽ 440

عَلَىٰ صِرَٰطٍۢ مُّسْتَقِيمٍۢ

በቀጥታም መንገድ ላይ ነህ፡፡

4
ጁዝ 22ገጽ 440

تَنزِيلَ ٱلْعَزِيزِ ٱلرَّحِيمِ

አሸናፊ አዛኝ ከሆነው አምላክ መወረድን ተወረደ፡፡

5
ጁዝ 22ገጽ 440

لِتُنذِرَ قَوْمًۭا مَّآ أُنذِرَ ءَابَآؤُهُمْ فَهُمْ غَٰفِلُونَ

አባቶቻቸው ያልተስፈራሩትን ሕዝቦች ልታስጠነቅቅበት (ተወረደ)፡፡ እነርሱ ዘንጊዎች ናቸውና፡፡

6
ጁዝ 22ገጽ 440

لَقَدْ حَقَّ ٱلْقَوْلُ عَلَىٰٓ أَكْثَرِهِمْ فَهُمْ لَا يُؤْمِنُونَ

በአብዛኞቻቸው ላይ ቃሉ በእውነት ተረጋገጠ፡፡ ስለዚህ እነርሱ አያምኑም፡፡

7
ጁዝ 22ገጽ 440

إِنَّا جَعَلْنَا فِىٓ أَعْنَٰقِهِمْ أَغْلَٰلًۭا فَهِىَ إِلَى ٱلْأَذْقَانِ فَهُم مُّقْمَحُونَ

እኛ በአንገቶቻቸው ላይ እንዛዝላዎችን አደረግን፡፡ እርሷም (እንዛዝላይቱ) ወደ አገጮቻቸው ደራሽ ናት፡፡ እነርሱም ራሶቻቸውን ያንጋጠጡ ናቸው፡፡

8
ጁዝ 22ገጽ 440

وَجَعَلْنَا مِنۢ بَيْنِ أَيْدِيهِمْ سَدًّۭا وَمِنْ خَلْفِهِمْ سَدًّۭا فَأَغْشَيْنَٰهُمْ فَهُمْ لَا يُبْصِرُونَ

ከስተፊታቸውም ግርዶን ከስተኋላቸውም ግርዶን አደረግን፡፡ ሸፈንናቸውም፡፡ ስለዚህ እነሱ አያዩም፡፡

9
ጁዝ 22ገጽ 440

وَسَوَآءٌ عَلَيْهِمْ ءَأَنذَرْتَهُمْ أَمْ لَمْ تُنذِرْهُمْ لَا يُؤْمِنُونَ

ብታሰጠነቅቃቸውም ባታስጠነቅቃቸውም በእነርሱ ላይ እኩል ነው፡፡ አያምኑም፡፡

10
ጁዝ 22ገጽ 440