LogoQuranEthiopia.com

ሱራ 44 · መካዊ

الدُّخَانِ

አድ-ዱኻን

ጭሱ · 59 አንቀጾች

۞

حمٓ

ሐ.መ (ሓ ሚም)፡፡

1
ጁዝ 25ገጽ 496

وَٱلْكِتَٰبِ ٱلْمُبِينِ

አብራሪ በኾነው መጽሐፍ እንምላለን፡፡

2
ጁዝ 25ገጽ 496

إِنَّآ أَنزَلْنَٰهُ فِى لَيْلَةٍۢ مُّبَٰرَكَةٍ ۚ إِنَّا كُنَّا مُنذِرِينَ

እኛ (ቁርኣኑን) በተባረከች ሌሊት ውስጥ አወረድነው፡፡ እኛ አስፈራሪዎች ነበርንና፡፡

3
ጁዝ 25ገጽ 496

فِيهَا يُفْرَقُ كُلُّ أَمْرٍ حَكِيمٍ

በውስጧ የተወሰነው ነገር ሁሉ ይልለያል፡፡

4
ጁዝ 25ገጽ 496

أَمْرًۭا مِّنْ عِندِنَآ ۚ إِنَّا كُنَّا مُرْسِلِينَ

ከእኛ ዘንድ የኾነ ትእዛዝ ሲኾን (አወረድነው)፡፡ እኛ (መልክተኞችን) ላኪዎች ነበርን፡፡

5
ጁዝ 25ገጽ 496

رَحْمَةًۭ مِّن رَّبِّكَ ۚ إِنَّهُۥ هُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلْعَلِيمُ

ከጌታህ በኾነው ችሮታ (ተላኩ)፡፡ እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡

6
ጁዝ 25ገጽ 496

رَبِّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَآ ۖ إِن كُنتُم مُّوقِنِينَ

የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ከኾነው (ተላኩ)፡፡ የምታረጋግጡ እንደኾናችሁ (ነገሩ እንዳልነው መኾኑን እወቁ)፡፡

7
ጁዝ 25ገጽ 496

لَآ إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ يُحْىِۦ وَيُمِيتُ ۖ رَبُّكُمْ وَرَبُّ ءَابَآئِكُمُ ٱلْأَوَّلِينَ

ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ ሕያው ያደርጋል፡፡ ይገድላልም፡፡ ጌታችሁ የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው፡፡

8
ጁዝ 25ገጽ 496

بَلْ هُمْ فِى شَكٍّۢ يَلْعَبُونَ

በእውነቱ እነርሱ የሚጫወቱ ሲኾኑ በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡

9
ጁዝ 25ገጽ 496

فَٱرْتَقِبْ يَوْمَ تَأْتِى ٱلسَّمَآءُ بِدُخَانٍۢ مُّبِينٍۢ

ሰማይም በግልጽ ጭስ የምትመጣበትን ቀን ተጠባበቅ፡፡

10
ጁዝ 25ገጽ 496