LogoQuranEthiopia.com

ሱራ 69 · መካዊ

الحَاقَّةِ

አል-ሐቃ

ግዴታዋ · 52 አንቀጾች

۞

ٱلْحَآقَّةُ

እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡

1
ጁዝ 29ገጽ 566

مَا ٱلْحَآقَّةُ

አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት!

2
ጁዝ 29ገጽ 566

وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا ٱلْحَآقَّةُ

አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?

3
ጁዝ 29ገጽ 566

كَذَّبَتْ ثَمُودُ وَعَادٌۢ بِٱلْقَارِعَةِ

ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡

4
ጁዝ 29ገጽ 566

فَأَمَّا ثَمُودُ فَأُهْلِكُوا۟ بِٱلطَّاغِيَةِ

ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡

5
ጁዝ 29ገጽ 566

وَأَمَّا عَادٌۭ فَأُهْلِكُوا۟ بِرِيحٍۢ صَرْصَرٍ عَاتِيَةٍۢ

ዓድማ በኀይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ፡፡

6
ጁዝ 29ገጽ 566

سَخَّرَهَا عَلَيْهِمْ سَبْعَ لَيَالٍۢ وَثَمَٰنِيَةَ أَيَّامٍ حُسُومًۭا فَتَرَى ٱلْقَوْمَ فِيهَا صَرْعَىٰ كَأَنَّهُمْ أَعْجَازُ نَخْلٍ خَاوِيَةٍۢ

ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡

7
ጁዝ 29ገጽ 566

فَهَلْ تَرَىٰ لَهُم مِّنۢ بَاقِيَةٍۢ

ለእነርሱም ቀሪን ታያለህን?

8
ጁዝ 29ገጽ 566

وَجَآءَ فِرْعَوْنُ وَمَن قَبْلَهُۥ وَٱلْمُؤْتَفِكَٰتُ بِٱلْخَاطِئَةِ

ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡

9
ጁዝ 29ገጽ 567

فَعَصَوْا۟ رَسُولَ رَبِّهِمْ فَأَخَذَهُمْ أَخْذَةًۭ رَّابِيَةً

የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡

10
ጁዝ 29ገጽ 567