LogoQuranEthiopia.com

ሱራ 77 · መካዊ

المُرۡسَلَاتِ

አል-ሙርሰላት

የተላኩት · 50 አንቀጾች

۞

وَٱلْمُرْسَلَٰتِ عُرْفًۭا

ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣

1
ጁዝ 29ገጽ 580

فَٱلْعَٰصِفَٰتِ عَصْفًۭا

በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣

2
ጁዝ 29ገጽ 580

وَٱلنَّٰشِرَٰتِ نَشْرًۭا

መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣

3
ጁዝ 29ገጽ 580

فَٱلْفَٰرِقَٰتِ فَرْقًۭا

መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣

4
ጁዝ 29ገጽ 580

فَٱلْمُلْقِيَٰتِ ذِكْرًا

መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣

5
ጁዝ 29ገጽ 580

عُذْرًا أَوْ نُذْرًا

ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡

6
ጁዝ 29ገጽ 580

إِنَّمَا تُوعَدُونَ لَوَٰقِعٌۭ

ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡

7
ጁዝ 29ገጽ 580

فَإِذَا ٱلنُّجُومُ طُمِسَتْ

ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡

8
ጁዝ 29ገጽ 580

وَإِذَا ٱلسَّمَآءُ فُرِجَتْ

ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡

9
ጁዝ 29ገጽ 580

وَإِذَا ٱلْجِبَالُ نُسِفَتْ

ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡

10
ጁዝ 29ገጽ 580