ٱقْرَأْ بِٱسْمِ رَبِّكَ ٱلَّذِى خَلَقَ
አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡
1
ጁዝ 30ገጽ 597
ሱራ 96 · መካዊ
የረጋ ደሙ · 19 አንቀጾች
ٱقْرَأْ بِٱسْمِ رَبِّكَ ٱلَّذِى خَلَقَ
አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡
خَلَقَ ٱلْإِنسَٰنَ مِنْ عَلَقٍ
ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡
ٱقْرَأْ وَرَبُّكَ ٱلْأَكْرَمُ
አንብብ፤ ጌታህ በጣም ቸር ሲኾን፤
ٱلَّذِى عَلَّمَ بِٱلْقَلَمِ
ያ በብርዕ ያስተማረ፡፡
عَلَّمَ ٱلْإِنسَٰنَ مَا لَمْ يَعْلَمْ
ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን፡፡
كَلَّآ إِنَّ ٱلْإِنسَٰنَ لَيَطْغَىٰٓ
በእውነቱ ሰው ወሰንን ያልፋል፡፡
أَن رَّءَاهُ ٱسْتَغْنَىٰٓ
ራሱን የተብቃቃ (ባለ ሀብት) ኾኖ ለማየቱ፡፡
إِنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلرُّجْعَىٰٓ
መመለሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
أَرَءَيْتَ ٱلَّذِى يَنْهَىٰ
አየህን? ያንን የሚከለክለውን፡፡
عَبْدًا إِذَا صَلَّىٰٓ
ባሪያን በሰገደ ጊዜ፤