إِذَا ٱلشَّمْسُ كُوِّرَتْ
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
1
ጁዝ 30ገጽ 586
ሱራ 81 · መካዊ
መጠቅለሉ · 29 አንቀጾች
إِذَا ٱلشَّمْسُ كُوِّرَتْ
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلنُّجُومُ ٱنكَدَرَتْ
ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْجِبَالُ سُيِّرَتْ
ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْعِشَارُ عُطِّلَتْ
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْوُحُوشُ حُشِرَتْ
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْبِحَارُ سُجِّرَتْ
ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلنُّفُوسُ زُوِّجَتْ
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْمَوْءُۥدَةُ سُئِلَتْ
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
بِأَىِّ ذَنۢبٍۢ قُتِلَتْ
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
وَإِذَا ٱلصُّحُفُ نُشِرَتْ
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤