LogoQuranEthiopia.com

ሱራ 80 · መካዊ

عَبَسَ

ዐበሰ

ፊቱን አጨፈገገ · 42 አንቀጾች

۞

عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ

ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡

1
ጁዝ 30ገጽ 585

أَن جَآءَهُ ٱلْأَعْمَىٰ

ዕውሩ ስለ መጣው፡፡

2
ጁዝ 30ገጽ 585

وَمَا يُدْرِيكَ لَعَلَّهُۥ يَزَّكَّىٰٓ

ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡

3
ጁዝ 30ገጽ 585

أَوْ يَذَّكَّرُ فَتَنفَعَهُ ٱلذِّكْرَىٰٓ

ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡

4
ጁዝ 30ገጽ 585

أَمَّا مَنِ ٱسْتَغْنَىٰ

የተብቃቃው ሰውማ፤

5
ጁዝ 30ገጽ 585

فَأَنتَ لَهُۥ تَصَدَّىٰ

አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡

6
ጁዝ 30ገጽ 585

وَمَا عَلَيْكَ أَلَّا يَزَّكَّىٰ

ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡

7
ጁዝ 30ገጽ 585

وَأَمَّا مَن جَآءَكَ يَسْعَىٰ

እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤

8
ጁዝ 30ገጽ 585

وَهُوَ يَخْشَىٰ

እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤

9
ጁዝ 30ገጽ 585

فَأَنتَ عَنْهُ تَلَهَّىٰ

አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡

10
ጁዝ 30ገጽ 585