LogoQuranEthiopia.com

ሱራ 87 · መካዊ

الأَعۡلَىٰ

አል-አዕላ

ላዕላዩ · 19 አንቀጾች

۞

سَبِّحِ ٱسْمَ رَبِّكَ ٱلْأَعْلَى

ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡

1
ጁዝ 30ገጽ 591

ٱلَّذِى خَلَقَ فَسَوَّىٰ

የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡

2
ጁዝ 30ገጽ 591

وَٱلَّذِى قَدَّرَ فَهَدَىٰ

የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡

3
ጁዝ 30ገጽ 591

وَٱلَّذِىٓ أَخْرَجَ ٱلْمَرْعَىٰ

የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡

4
ጁዝ 30ገጽ 591

فَجَعَلَهُۥ غُثَآءً أَحْوَىٰ

(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡

5
ጁዝ 30ገጽ 591

سَنُقْرِئُكَ فَلَا تَنسَىٰٓ

(ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡

6
ጁዝ 30ገጽ 591

إِلَّا مَا شَآءَ ٱللَّهُ ۚ إِنَّهُۥ يَعْلَمُ ٱلْجَهْرَ وَمَا يَخْفَىٰ

አላህ ከሻው ነገር በስተቀር፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡

7
ጁዝ 30ገጽ 591

وَنُيَسِّرُكَ لِلْيُسْرَىٰ

ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡

8
ጁዝ 30ገጽ 591

فَذَكِّرْ إِن نَّفَعَتِ ٱلذِّكْرَىٰ

ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡

9
ጁዝ 30ገጽ 591

سَيَذَّكَّرُ مَن يَخْشَىٰ

(አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡

10
ጁዝ 30ገጽ 591