وَٱلْفَجْرِ
በጎህ እምላለሁ፡፡
1
ጁዝ 30ገጽ 593
ሱራ 89 · መካዊ
ጎሁ · 30 አንቀጾች
وَٱلْفَجْرِ
በጎህ እምላለሁ፡፡
وَلَيَالٍ عَشْرٍۢ
በዐሥር ሌሊቶችም፡፡
وَٱلشَّفْعِ وَٱلْوَتْرِ
በጥንዱም በነጠላውም፡፡
وَٱلَّيْلِ إِذَا يَسْرِ
በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡
هَلْ فِى ذَٰلِكَ قَسَمٌۭ لِّذِى حِجْرٍ
በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?
أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِعَادٍ
ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?
إِرَمَ ذَاتِ ٱلْعِمَادِ
በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡
ٱلَّتِى لَمْ يُخْلَقْ مِثْلُهَا فِى ٱلْبِلَٰدِ
በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡
وَثَمُودَ ٱلَّذِينَ جَابُوا۟ ٱلصَّخْرَ بِٱلْوَادِ
በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡
وَفِرْعَوْنَ ذِى ٱلْأَوْتَادِ
በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡