وَٱلضُّحَىٰ
በረፋዱ እምላለሁ፡፡
1
ጁዝ 30ገጽ 596
ሱራ 93 · መካዊ
ረፋዱ · 11 አንቀጾች
وَٱلضُّحَىٰ
በረፋዱ እምላለሁ፡፡
وَٱلَّيْلِ إِذَا سَجَىٰ
በሌሊቱም ጸጥ ባለ ጊዜ፤
مَا وَدَّعَكَ رَبُّكَ وَمَا قَلَىٰ
ጌታህ አላሰናበተህም፤ አልጠላህምም፡፡
وَلَلْءَاخِرَةُ خَيْرٌۭ لَّكَ مِنَ ٱلْأُولَىٰ
መጨረሻይቱም (ዓለም) ከመጀመሪያይቱ ይልቅ ላንተ በላጭ ናት፡፡
وَلَسَوْفَ يُعْطِيكَ رَبُّكَ فَتَرْضَىٰٓ
ጌታህም ወደ ፊት (ብዙን ስጦታ) በእርግጥ ይሰጥሃል፡፡ ትደሰታለህም፡፡
أَلَمْ يَجِدْكَ يَتِيمًۭا فَـَٔاوَىٰ
የቲም ኾነህ አላገኘህምና አላስጠጋህምን? (አስጠግቶሃል)፡፡
وَوَجَدَكَ ضَآلًّۭا فَهَدَىٰ
የሳትክም ኾነህ አገኘህ መራህም፡፡
وَوَجَدَكَ عَآئِلًۭا فَأَغْنَىٰ
ድኻም ኾነህ አገኘህ፤ አከበረህም፡፡
فَأَمَّا ٱلْيَتِيمَ فَلَا تَقْهَرْ
የቲምንማ አትጨቁን፡፡
وَأَمَّا ٱلسَّآئِلَ فَلَا تَنْهَرْ
ለማኝንም አትገላምጥ፡፡