LogoQuranEthiopia.com

ሱራ 99 · መዲናዊ

الزَّلۡزَلَةِ

አዝ-ዘልዘላ

የመሬት መንቀጥቀጡ · 8 አንቀጾች

۞

إِذَا زُلْزِلَتِ ٱلْأَرْضُ زِلْزَالَهَا

ምድር (በኀይል) መንቀጥቀጥዋን በተንቀጠቀጠች ጊዜ፤

1
ጁዝ 30ገጽ 599

وَأَخْرَجَتِ ٱلْأَرْضُ أَثْقَالَهَا

ምድር ሸክሞችዋን ባወጣችም ጊዜ፤

2
ጁዝ 30ገጽ 599

وَقَالَ ٱلْإِنسَٰنُ مَا لَهَا

ሰውም ምን ኾነች? ባለ ጊዜ፤

3
ጁዝ 30ገጽ 599

يَوْمَئِذٍۢ تُحَدِّثُ أَخْبَارَهَا

በዚያ ቀን ወሬዎችዋን ትናገራለች፡፡

4
ጁዝ 30ገጽ 599

بِأَنَّ رَبَّكَ أَوْحَىٰ لَهَا

ጌታህ ለእርሷ በማሳወቁ ምክንያት፡፡

5
ጁዝ 30ገጽ 599

يَوْمَئِذٍۢ يَصْدُرُ ٱلنَّاسُ أَشْتَاتًۭا لِّيُرَوْا۟ أَعْمَٰلَهُمْ

በዚያ ቀን ሰዎች ሥራዎቻቸውን (ምንዳዋን) እንዲያዩ ይደረጉ ዘንድ (እንደየሥራቸው) የተለያዩ ኾነው (ከመቆሚያው ስፍራ) ይመለሳሉ፡፡

6
ጁዝ 30ገጽ 599

فَمَن يَعْمَلْ مِثْقَالَ ذَرَّةٍ خَيْرًۭا يَرَهُۥ

የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡

7
ጁዝ 30ገጽ 599

وَمَن يَعْمَلْ مِثْقَالَ ذَرَّةٍۢ شَرًّۭا يَرَهُۥ

የብናኝ ክብደት ያክልም ክፉን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡

8
ጁዝ 30ገጽ 599